Wednesday, February 11, 2015

እጅግ የላቀው የእግዚአብሔር መገለጥ፤
ትምህርተ ክርስቶስ
መግቢያ፡- እኛ ክርስቲያኖች ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው የሆነውን አምላካችንን የናዝሬቱን ኢየሱስን የምናመልክ ነን፡፡ ጌታን ኢየሱስን ማወቅ ደግሞ በክርስትና ሕይወት ቀዳሚውና የመጀመሪያው ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም ስለዚህ የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ በስፋት ያስተምራል፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ዋና ዋና ትምህርቶች ውስጥ የኢየሱስ ክርስቶስን መለኮታዊ ማንነትና ሰብዓዊ ማንነት በተመለከተ የሚሰጥ ትምህርት ማለትም ሚስጥረ ክርስቶስ በታሪክ ሁሉ ውስጥ በርካታ ክርክሮች ሲያስተናግድ የነበረ ርዕሰ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ርዕስ ካለው አስፈላጊነትና ካስተናገዳቸው ልዩ ልዩ የአመለካከት ውዝግቦች አንጻር በዚህ አጭር ጽሑፍ ለመዳሰስ የተሞከረው የምዕመናንን መንፈሳዊ መረዳት ለማሳደግ ጠቀሜታ እንደሚኖረው የታመነበትን ጥቂቱን ብቻ ነው፡፡ ጽሑፉ  በዮሐንስ 1.14 ‹ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።›  በሚለው ቃል ላይ የተመሰረተ ሲሆን “እጅግ የላቀው የእግዚአብሔር መገለጥ” በተሰኘ ርዕስ እንመለከተዋለን፤ ይህ ጥቅስ በሌላ አማራጭ ትርጉም ‹ክርስቶስም በዚህ በምድር ከእኛ ጋር ሊኖር አፍቃሪ የሆነ ይቅርታንና እውነትን ተሞልቶ ሰው ሆነ› በሚል ተተርጉሞአል፡፡ ጽሑፉም ሌሎች በርካታ ቅዱሳት መጻሕፍት የንባብ ክፍሎችን በማካተት በስምንት ተከታታይ የትምህርት ክፍሎች የሚሸፈን ነው፡፡ የጽሑፉም አቀራረብ ሥነ መለኮታዊ ዘገባ (Information) መስጠት ሳይሆን ትምሕርተ ክርስቶስ በያዘው ሥነ መለኮት ውስጥ ከህይወታችን ጋር ሊዛመድ የሚገባውን እውነት ማመልከት ነው፡፡ እግዚአብሔር የቃሉን ደጃፍ ይክፈትልን!! አሜን፡፡ 
በጽሑፉ የምንመለከታቸው ስምንት ክፍሎች የሚከተለውን ይመስላሉ፡-
ክፍል 1 ሎጎስ
ክፍል 2 ሀ. ቃልም ሥጋ ሆነ
ክፍል 3 ለ. አምላክ ሰው መሆኑ
ክፍል 4 ሐ. በመለኮቱና በትስብዕቱ መካከል ያለው ግንኙነት
ክፍል 5 ክብሩ
ክፍል 6 የባሕርይ ልጅ
ክፍል 7 የመለኮት መገለጫ ባህርይ
ክፍል 8 የእግዚአብሔር መገለጥ

                                                                                  አዘጋጅ ግዛቸው ከበደ /ቄስ/


‹‹ቃልም ሥጋ ሆነ››
                   ክፍል አንድ ሎጎስ
‹‹ቃሉ››
ዮሐንስ 1.14 በቅዱሳት መጻሕፍት ካሉ ጥቅሶች ሁሉ ያለ ጥርጥር እጅግ አስገራሚው ነው፡፡ ይህ ጥቅስ ከአንድ ጊዜ በላይ ደጋግመን ልንመለከተው የሚያስፈልገንን እጅግ የከበረ አስገራሚ የእውነት መዝገብ ታጭቆበታል፡፡ ለመነሻ እንዲሆነን አንዱን ቃል መዘን እንመልከት ‹‹ቃልም …››
1. ‹ቃሉ› (ቃልን መረዳት)
ስለዚህ ጉዳይ ልብ መባል ያለበት ጉዳይ አለ፡፡ ይኸውም ቁጥር 1 የሚለውን በጥንቃቄ ካልተረዳን ቁ 14 ምን እንደሚል በትክክል መረዳት አለመቻሉ ነው፡፡ በተለይም ‹ቃል› የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ አስፈላጊነት መረዳት አለብን፡፡ ቃል በቀጥታ ክርስቶስ ማለት ነው፣ እርሱም የእግዚአብሔር ጥበብና ሃይል ነው፣ እግዚአብሔር ለሰው ያለው የግሉ አካላዊ መታየትና መገለጥ ነው፡፡

ከቁጥር 2-13 ለመብራራት እንደተሞከረው የሐዋርያው ሃሳብ ግልጽ ነው፤ ‹‹በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ (ቃልም ከእግዚአብሔር ጋር ነበር /አመት/) ቃልም እግዚአብሔር ነበረ ….ቃልም ሥጋ ሆነ….››
አስቀድመን የዮሐንስ ወንጌል ሲጻፍ በምን ዓላማ እንደተጻፈ ማየት ጠቃሚ ነው፡፡ በዮሐንስ 20.30-31 ‹ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል› በሚለው መሰረት አይሁድ የሆኑትንና ያልሆኑትን ሁለቱንም ወገኖች በጽሁፎቹ ወደ እምነት መምራት ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈበት ዓላማ ነው፡፡ አይሁድን በተመለከተ በእርግጥም ኢየሱስ ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው መሲሁ ክርስቶስ መሆኑን እንዲያምኑ አይሁድ ያልሆኑትን በተመለከተ ደግሞ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እና እግዚአብሔር ወልድ መሆኑን እንዲረዱ ነው፡፡
ሐዋርያው ስለ ኢየሱስ መጻፍ ሲጀምር ዋናውን ሃሳብ እየነካ ለጽሑፉ መግቢያ በሚሰጥበት ጊዜ፣ በዚያው መጠን ግዙፍ ከሆኑ እውነቶች ጋር ይገናኛል፡፡  በመንፈስ ቅዱስ ከተመራ ጥንቃቄ ጋር ‹ክርስቶስ› እና ወይም ‹የእግዚአብሄር ልጅ› የሚሉት ቃላት ለአንባቢዎቹ ከበድ ያሉ ሃሳቦች በመሆናቸው መግቢያው እነዚህን ቃላት ወይም ሐረጎች እንዲያካትት አላደረገም፡፡ ሆኖም ጽሑፉን እየገፋ ሲሄድ ከነዚያ ቃላትና ሃሳቦች መካከል አንዳቸውንም ሊተዋቸው ምንም ፍላጎት አልነበረውም፡፡

አይሁድ የሚጠባበቁት፡- አይሁድ ዮሐንስ “ቃል” እያለ ስለ ክርስቶስ መጻፉን ሲያውቁ በእርግጥም ጆሮአቸውን ይሰጣሉ፡፡ ነገር ግን እነርሱ መሲሁን የሚጠብቁት ከሆነ ምድራዊ ተልእኮ ጋር ከተያያዘ የፖለቲካ ዓላማ ጋር ነበር፡፡ እንግዲህ ዮሐንስ የእነርሱን ጆሮ መግኘቱ እጅግ አስፈላጊ የሚሆነው ኢየሱስ እውነተኛ አምላክ መሆኑን ማወቅ ስላለባቸው ነው፡፡
የአህዛብ ግምት፡- ለአህዛብም ቢሆን ‹የእግዚአብሔር ልጅ› ስለመባሉ  በሚያነቡበት ጊዜ ከአማልክት መካከል አንዱ ከአንዲት ምድራዊት ሴት ጋር ባደረገው ግንኙነት ስለ ተወለደ አንድ ሰው ሊገምቱና ሊስቡ ይችሉ ይሆናል - ይህ አይነቱ አስተሳሰብ በግሪካውያን ተረት  የተለመደ አህዛባዊ አስተሳሰብ ነው፡፡
የዮሐንስ ሸክም፡- ዮሐንስ ሊያስተላልፍ የፈለገው መልዕክት እርሱ የሚጽፍለት “ቃል” የተባለው ሰው ፈጽሞ የተለየና የከበረ መሆኑን አንባቢዎቹ እርግጠኛ ሆነው እንዲረዱ ነው - እርሱ ከብዙዎች አንዱ አይደለም፣ ሌላ መሲህም አይደለም፣ ማንኛውም ክርስቶስ አይደለም፤ በእርግጥም ሌላ የአህዛብ ጣኦት አይደለም፡፡ ለዚህ ነው ሐዋርያው ጌታ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እና የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ማብራራት ከመጀመሩ በፊት ስለ እርሱ የሚጽፍለት “ቃል” የተባለው ይህ ሰው በእውነትና በሙላት ራሱ እግዚአብሔር የመሆኑን ነጥብ በግልጽና በማያሻማ መንገድ እንቅጩን የሚናገረው፡፡
2. የተሳሳተ ግንዛቤን ለማስወገድ የተመረጠ መጠሪያ ‹ቃል›
የሆነ ሆኖ የትኛውንም የተሳሳተ ግንዛቤ ለማስወገድ በመጀመርያ ዋነኛ ማንነቱን በሚገልጥ ስያሜ ይጠራዋል፤ ‹ክርስቶስ› ወይም ‹የእግዚአብሔር ልጅ› ብሎ ሳይሆን በሌላ አይነተኛ ስም ይገልጠዋል፡፡ ዮሐንስ በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ የመረጠው ተገቢ የሆነ ስያሜ ‹ቃል› (በግሪኩ ‹ሎጎስ›) የሚል ነው፡፡
ቃል ለአይሁድ፣ ቃል ለአህዛብ፡- /በአመት የጥናት መግለጫ ‹‹ግሪኮች ‹ቃል› የተሰኘውን የሓሳብ መግለጫ ለተነገረው ፣ ለተሰማው ብቻ ሳይሆን፣ ላልተነገረው ላልተሰማውና ገና በአእምሮ ውስጥ ላለው ሓሳብ ጭምር ይጠቀሙበታል፡፡ ፍጥረተ አለምን በተመለከተ ሲጠቀሙበት ግን የፍጥረትን ሥርዓት የሚመራውን ሕግ በማሰብ ነው፡፡ አይሁድ ግን ‹ቃል› የሚለውን የሓሳብ መግለጫ የሚጠቀሙበት እግዚአብሔርን በተመለከተ ነው፡፡ ስለዚህም ዮሐንስ የተጠቀመው አይሁድም ሆኑ አሕዛብ በሚረዱት ቃል ነው፣››ይላል፡፡/ ለአይሁድም ሆነ ለግሪክ ይህ ቃል ትርጉም የሚሰጥ ነው፡፡ ከሌሎች ቃላት ሁሉ ይልቅ ‹ሎጎስ› ለሁለቱም አይነት አንባቢዎች አዕምሮ ሰፊ ሃሳብን አጭቆ ይዞአል፡፡
ቃል በግሪክ ፍልስፍና ውስጥ፡- በአረማውያን ዘንድ “ሎጎስ” በሚለው ቃል የሚገለጠው ጽንሰ ሃሳብ በእጅጉ ተለመደና የታወቀ ነው፡፡ ግሪካዊው ፈላስፋ ሂራክሊቱስ (600 ቅክ) ሎጎስ የአጥናፍ አለም ነፍስ ነው ብሎ ያስባል- ይኸውም ሁሉም ነገር የተሰራበትና የሆነበት፣ ሁሉንም ነገር ጠብቆ የያዘ፣ እንዲሁም የመላውን ዩኒቨርስ ሚዛን የሚጠብቅ ፈጣሪ ነው ማለት ነው፡፡
የጠቢባኑ ግንዛቤ፡- በዘመኑ ያሉ ጠቢባን ሃሳቡን ሰፋ አድርገው ያዩታል፡፡ ለእነርሱም ሎጎስ በአንድ ጊዜ በሁሉም ስፍራ የሚገኝ (omnipresent) ጥበብ ሲሆን በእርሱም ሁሉ እንደተፈጠረና እንደሚመራ ያስባሉ፡፡
አረማውያን ሎጎስን ከታላቁ አምላክ ጋር ያያይዙታል፡፡ ስለዚህ ዮሐንስ የእርሱ የቃል ምርጫ ለአሕዛባዊ አንባቢዎቹ የሚያረጋግጥላቸው እየጻፈ ያለው ስለ ሁሉን ቻይ እና ለሁሉ ስለሚበቃ፣ የሁሉ ጀማሪ ስለሆነ፣ የሁሉ መሰረትና ምክንያት በመሆን ለራሱ ግን የመሆን ምክንያት ስለሌለው፣ በራሱ የሆነ ስለሆነው ማንነት እንደሆነ ነው፡፡
አይሁድም ፣ ‹ሎጎስ› የሚለው ቃል ከያዘው ጽንሰ ሃሳብ ጋር ጠንካራ የሆነ ግንኙነት አላቸው፡፡ ለእነርሱም የዮሐንስ የመግቢያ ቃላት ማለትም ቁጥር 1 የዘፍጥረትን ‹በመጀመሪያ…› የሚለውን ቃል የሚያስታውሳቸው ነው፡፡ በእርግጥም “ሎጎስ”፣ ወይም “ቃል” የሚለው ጽንሰ ሃሳብ እግዚአብሔር አለምን እንዴት እንደ ፈጠረ ያስታውሳቸዋል፣ ‹‹እግዚአብሔርም አለ›› የሚለው መግለጫ በዘፍጥረት 1 ላይ ዘጠኝ ጊዜ ተጠቅሶአል፡፡  “ሎጎስ” ለአይሁድ በእውነትም የእግዚአብሄር የሆነ “ሁሉን ቻይ ፈጣሪ ቃል” ትርጉም ነው፡፡
የቅዱሳት መጻሕፍት ማስረጃ፡- በመዝሙር 33. 6፣9 ‹‹በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ…..እርሱ ተናግሮአልና፥ ሆኑም እርሱ አዘዘ፥ ጸኑም።›› የሚል እናነባለን፡፡ በኢሳያስ 55. 11 ‹‹ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል የምሻውን ያደርጋል የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም።›› ይላል፡፡ እግዚአብሔር ሲናገር አንድ ነገር እንደሚያደርግና እንደሚሆን እነዚህ ጥቅሶች ግልጽ ያደርጉልናል፡፡ አይሁድ ሎጎስ የተሰኘውን ቃል ከአምላካዊ ተግባር ጋር እንደሚያያይዙት በዚህ ማየት ይቻላል፡፡
ከዚህም በላይ አይሁድ ‹ያህዌ› የተሰኘውን የእግዚአብሔርን ሥም ሲያነሱ፣ ስለ እርሱም በሚናገሩበት ጊዜ፣ ስሙን መጥራት እርሱን እንደ አለማክበር ስለሚቆጥሩ በሌሎች አማራጭ ቃላትና መጠሪያዎች እርሱን መጥራት ይመርጣሉ፡፡ እንደ ‹ቅዱሱ›፣ ‹ስሙ›፣ ወይም ‹ቃል› ያሉትን ይጠቀማሉ፡፡ ስለዚህም  “ቃል” ለአይሁድ ሥነ መለኮት “ያህዌ” ነው፡፡ ዮሐንስ ‹ሎጎስ› የሚለውን ቃል በመጠቀሙ  ለአይሁድ አንባቢያኑ የሚነግራቸው “እኔ የምጽፍለት እርሱ ሃያሉ እና ቅዱሱ የሰማይና የምድር ፈጣሪ ነው”፣ እያለ ነው፡፡
3. የቃሉ መወድስ
ከቁጥር 14 በፊት ባሉት ቁጥሮች ውስጥ ዮሐንስ ስለ ቃሉ የተነገሩ  ወደ 8 የሚደርሱ የመወድስ ዓረፍተ ነገሮችን አስቀምጦአል፣ እያንዳንዳቸውም ለማንኛውም የአይሁድና የግሪክ ሰዎች አስተሳሰብ ተቀባይነት ያላቸው ናቸው፡፡
1ኛ/ ‹በመጀመሪያ ቃል ነበረ› (ቁ 1) በሌላ አባባል፣ ጊዜና ያለው ነገር ሁሉ ወደ መኖር ሲመጣ፣ ቃል ቀድሞውኑ እየኖረ ነበር፡፡ ከዘላለም ጀምሮ እርሱ በዚያ ነበር፡፡ ማንኛውም ነገር ሕልውና ከማግኘቱ በፊት ቃል ነበር፡፡

2ኛ/ ‹ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ›(ቁ 1) ቃሉ ሁልጊዜ ከእግዚአብሄር ጋር ነበረ፡፡ ከዘላለም ሁሉ በፊት በመካከላቸው (በእግዚአብሔርና በቃሉ መካከል) የማይከፈል አንድነት ነበራቸው፡፡

3ኛ/ ‹ቃልም እግዚአብሔር ነበረ›(ቁ 1) አዎ ቃሉ ከእግዚአብሔር ተለይቶ በራሱ ማንነት ይታወቃል፣ ነገር ግን የተፈጠረ ነገር (ፍጡር) አይደለም፡፡ በእርግጥ ከዘላለም በፊት እግዚአብሔር ሆኖ ኖሮአል፡፡ ዮሐንስ እዚህ ላይ በሥላሴዎች መካከል ያለውን ልዩነት በደንብ ይነካል፡፡ ነገር ግን ማናቸውም የማያምኑ የሆኑ አንባቢዎች ይህንን አይረዱትም፡፡

4ኛ/ ‹ሁሉ በእርሱ ሆነ›/ ‹ዓለሙም በእርሱ ሆነ›(ቁ 3ና10) እርሱ የዚህ አጥናፍ አለም (universe) ፈጣሪ ነው፣ የሚለው ዓረፍተ ነገር ለአይሁድም ሆነ ለግሪክ ሰዎች የሚያስቸግራቸው አይደለም፡፡

5ኛ/ ‹በእርሱ ሕይወት ነበረች› (ቁ4) ሕይወት ሰጪ እና የሁሉ ነገር ምንጭ ከሆነው ቃል ህይወትን ያልተቀበለ ሕያው ፍጡር በፍጥረተ ዓለም ውስጥ የለም፡፡ ፍጥረት ሁሉ ሕያው የሆነው በእርሱ ሕይወት ነው፡፡

6ኛ/ ‹ሕይወትም የሰው ብርሐን ነበረች/ ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሐን…›(ቁ4፣9) ከእርሱ የተገኘች ሕይወት ለሰው ልጅ ሁሉ የምታበራ ብርሃን ናት፡፡ ዮሐንስ እዚህ ላይ እየተናገረ ያለው ቃሉ የእግዚአብሔር መገለጠ/ እግዚአብሔርን የሚገልጠው የመሆኑን እውነታ ነው፡፡ ነገር ግን አይሁድ በምሳሌ ምዕራፍ 8 ብርሃን ቃሉን በአካላዊ ማንነቱ እንዳለ ጥበብ ሲመለከቱት አሕዛብ ግን ዓረፍተ ነገሩን በፍልስፍናቸው የተረጉሙታል፡፡

7ኛ/ ‹የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም› (ቁ 11) እዚህ ላይ አንባቢዎቹ ይስማማሉ፣ በእኛ ዘንድ ሁልጊዜ ፈጽሞ የማያስተውሉና የማያስቡ ሞኞች አሉ ይላሉ፡፡

8ኛ/ ያም ሆኖ የሚቀበሉት ደግሞ አሉ ‹ለተቀበሉት…›(ቁ 12) ለሚያምኑበት፣ ለሚቀበሉትና ለሚያመልኩት አንባቢዎቹ በዚህ እንኳን ደስ ያላችሁ ሊባሉና በዚህ ደስ ሊላቸው ገባቸዋል፡፡

በእርግጥም የመጽሐፉን ዋነኛ ገጸ ባህርይ ለአንባቢዎቹ እንዲህ ባለ ተስማሚና ተቀባይነት ባለው አቀራረብ መግቢያ መስጠት የቻለ ጸሐፊ የለም፡፡
ማጠቃለያ
በአዲስ ኪዳን ውስጥ በክርስቶስ መለኮትነት ላይ የተሰጠውን ጠንካራ ትምሀርት እንዳንስተው መጠንቀቅ አለብን፡፡

ስለ እርሱን በተመለከተ  ከገጠሪቱ ናዝሬት እንደ ተነሳ ተራ እንደሆነ አንድ ድንቅ ሰው ማሰብ ሊቀል ይችል ይሆናል፣ በኖረው የፍቅርና ሌሎችን የመንከባከብ ምሳሌ ድንቅ የሆኑ የሕይወት ምሳሌዎችን እና ተሞክሮዎችን እንደተወልን አንድ አስገራሚ ሰው እናየው ይሆናል፡፡ አዎ በእርግጥም ቃሉ በታሪካችን ውስጥ ገብቶ ሥጋ ሆኖአል፣ እኛን መስሎአል፣ ደግሞም ፍጹም ሰው ነበር እስከ አሁንም ድረስ ነው፣ ነገር ግን ሐዋርያው ዮሐንስ በመንፈስ ቅዱስ በመነዳት ከሰጠው ከዚህ ጠንካራ አጽንዖት ውጭ ወንጌላዊ የሆነው አስተምህሮተ ክርስቶሳችን በቀላሉ ሰውን ወደ አማከለ ተራ ደረጃ ማለትም  ከመጽሐፍ ቅዱሳዊው መገለጥ ጋር ፈጽሞ ወደማይታረቅበት ደረጃ ወርዳል፡፡
በመካከለኛው ዘመን ሥነ ጥበብ በተሰሩ፣ ስሜትን የሚነካ የከሳና የገረጣ ፊት ባላቸው ወይም በእጅጉ ተውበው በደመቁ ኃይማኖታዊ በሆኑ ኢየሱሳዊ ሥዕላ ሥዕሎች ላይ የተመሰረተ የዛሬ ስብከት ማንንም ሊያድን አይችልም፡፡ በጣም በእርግጠኝነት መናገር እንደሚቻለው እንዲህ ያለው ሰው ሰራሽ የሆነ “ክርስቶስ” ሐዋርያው ዮሐንስ በወንጌሉም ሆነ በራዕዩ የሚጽፍለት የነገስታት ንጉስና የጌታዎች ጌታ አይደለም፡፡
የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ያቀረቡልን ኢየሱስ እውነተኛ አምላክ፣ ደግሞም ሕያው ሰው መሆኑን በደንብ ማስታወስ አለብን፡፡ ስለዚህም ቃል የተባለው እርሱ የዮሐንስ አህዛባዊ አንባቢዎች ከሚመስላቸው አካል ካልሆነ አንድ መርህ ወይም ሃይል በላይ ያለ በራሱ የሚኖር ማንነት ነው፡፡
ሉቃስም ስለ ሐዋርያቱ ሲናገር ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት (ሉቃ 1.2) በማለት ‹ቃሉ› የሚለውን መግለጫ ይጠቀማል›፣ ፡፡ የሚናገረውው ስለ ጌታ ኢየሱስ ነው ወይንስ ሰለ ወንጌሉ? አንዳንድ ተርጓሚዎች ወንጌሉ ነው ሲሉ ከሁለተኛው ሃሳብ ጋር ቃሉን ለማዛመድ ሞክረዋል፣ ይሁንና ሉቃስ ሐዋርያቱን በተመለከተ ሲናገር ቃሉን ‹በዓይን ያዩት› ናቸው ይላል፣ የሚያመለክተውም ጌታ ኢየሱስን ነው፡፡ ይሁን እንጂ የቃሉ ‹አገልጋዮች› ብሎ ደግሞ ይጠራቸዋል፣ የኸውም ወንጌሉን ያመለክታል፡፡ ሐዋርያቱ ቃሉን ያዩት የቃሉ አገልጋዮች ናቸው፡፡
በጥንት ቤተከክርስቲያን ይህ አከራካሪ ጉዳይ አልነበረም፡፡ ምክንያቱም ለነዚያ ክርስቲያኖች ኢየሱስ ክርስቶስ የተባለው እርሱ በማንነቱ በእርግጥም የወንጌሉ የዘት ነበር፡፡
ይህ በትክክል ጳውሎስ ፤‹መቼም አይሁድ ምልክትን ይለምናሉ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ፥ እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን…› (1ቆሮ 1.22) ብሎ የተናገረለት ጉዳይ ነው፡፡ በገላትያ 3.1 ላይም ‹በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤› ይላል፡፡ስለዚህም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መናገር ማለት ለሐዋርያቱ በእውነትም የስብከታቸውን ይዘት የሚያመለክት ነው፡፡
ዮሐንስ በሚገርም አገላለጽ ይህንን ቃል “የሕይወት ቃል” ሲል ይጠራዋል፣ እርሱንም “ከመጀመሪያው የነበረውን የሰማነው በዓይኖቻችንም ያየነው የተመለከትነው እጆቻችንም የዳሰሱት” ይለዋል ጨምሮም “ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤” ሲል ሐዋርያቱ ከዚያ ቃል ጋር የነበራቸውን ቅርብ ግንኙነት ይመሰክራል፡፡
ከሞት የተነሳውን ሕያው የሆነና የከበረውን ክርስቶስ እያወቀ ያደገ ማንም ሰው ቢሆን፣ ሌላ ማንኛውንም ተራ ነገር ወይም ሌላ ማንንም ቢሆን ፈጽሞ ማወጅና መስበክ አይችልም- እጅግ ያነሰውን የስነ ምግባር መርህ ወይም መልካም ፈቃድን አልያም ደስ የሚል ድምጸት ያላቸውን ጥሩ ጥሩ አዝናኝ አባባሎችን በመስበክና በማወጅ ዘመኑን አያጠፋም፡፡ እንዲህ ላለ ሰብዓዊ ተራ ነገር ሐዋርያቱ ለመሞት አልተዘጋጁም ነበር፣ በእርግጥም እንደ ሰማዕት የሞቱለት ጉዳይ እንዲህ የወረደ ነገር አልነበረም፡፡ እስከሞት ድረስ ሰው ሆኖ በመካከላቸው ከእነርሱ ዘንድ ስላደረው አምላክ ከመናገርና እርሱን ከማምለክ ለአፍታም ቢሆን አላረፉም፡፡ በየዘመናቱ ሁሉ የተሰበከው ደግሞ እንዲሁ ነበር፡፡ አሁንም የሚሰበከው እንዲሁ ነው፡፡ ለዘላለሙም የሚሰበከው እንዲሁ ነው፡፡ አሜን!!

                                                                                 gizachewkr@gmail.com       


ትምህርተ ክርስቶስ መግቢያ እና ክፍል 1

እጅግ የላቀው የእግዚአብሔር መገለጥ፤
ትምህርተ ክርስቶስ
መግቢያ፡- እኛ ክርስቲያኖች ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው የሆነውን አምላካችንን የናዝሬቱን ኢየሱስን የምናመልክ ነን፡፡ ጌታን ኢየሱስን ማወቅ ደግሞ በክርስትና ሕይወት ቀዳሚውና የመጀመሪያው ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም ስለዚህ የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ በስፋት ያስተምራል፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ዋና ዋና ትምህርቶች ውስጥ የኢየሱስ ክርስቶስን መለኮታዊ ማንነትና ሰብዓዊ ማንነት በተመለከተ የሚሰጥ ትምህርት ማለትም ሚስጥረ ክርስቶስ በታሪክ ሁሉ ውስጥ በርካታ ክርክሮች ሲያስተናግድ የነበረ ርዕሰ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ርዕስ ካለው አስፈላጊነትና ካስተናገዳቸው ልዩ ልዩ የአመለካከት ውዝግቦች አንጻር በዚህ አጭር ጽሑፍ ለመዳሰስ የተሞከረው የምዕመናንን መንፈሳዊ መረዳት ለማሳደግ ጠቀሜታ እንደሚኖረው የታመነበትን ጥቂቱን ብቻ ነው፡፡ ጽሑፉ  በዮሐንስ 1.14 ‹ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።›  በሚለው ቃል ላይ የተመሰረተ ሲሆን “እጅግ የላቀው የእግዚአብሔር መገለጥ” በተሰኘ ርዕስ እንመለከተዋለን፤ ይህ ጥቅስ በሌላ አማራጭ ትርጉም ‹ክርስቶስም በዚህ በምድር ከእኛ ጋር ሊኖር አፍቃሪ የሆነ ይቅርታንና እውነትን ተሞልቶ ሰው ሆነ› በሚል ተተርጉሞአል፡፡ ጽሑፉም ሌሎች በርካታ ቅዱሳት መጻሕፍት የንባብ ክፍሎችን በማካተት በስምንት ተከታታይ የትምህርት ክፍሎች የሚሸፈን ነው፡፡ የጽሑፉም አቀራረብ ሥነ መለኮታዊ ዘገባ (Information) መስጠት ሳይሆን ትምሕርተ ክርስቶስ በያዘው ሥነ መለኮት ውስጥ ከህይወታችን ጋር ሊዛመድ የሚገባውን እውነት ማመልከት ነው፡፡ እግዚአብሔር የቃሉን ደጃፍ ይክፈትልን!! አሜን፡፡ 
በጽሑፉ የምንመለከታቸው ስምንት ክፍሎች የሚከተለውን ይመስላሉ፡-
ክፍል 1 ሎጎስ
ክፍል 2 ሀ. ቃልም ሥጋ ሆነ
ክፍል 3 ለ. አምላክ ሰው መሆኑ
ክፍል 4 ሐ. በመለኮቱና በትስብዕቱ መካከል ያለው ግንኙነት
ክፍል 5 ክብሩ
ክፍል 6 የባሕርይ ልጅ
ክፍል 7 የመለኮት መገለጫ ባህርይ
ክፍል 8 የእግዚአብሔር መገለጥ

                                                                                  አዘጋጅ ግዛቸው ከበደ /ቄስ/


‹‹ቃልም ሥጋ ሆነ››
                   ክፍል አንድ ሎጎስ
‹‹ቃሉ››
ዮሐንስ 1.14 በቅዱሳት መጻሕፍት ካሉ ጥቅሶች ሁሉ ያለ ጥርጥር እጅግ አስገራሚው ነው፡፡ ይህ ጥቅስ ከአንድ ጊዜ በላይ ደጋግመን ልንመለከተው የሚያስፈልገንን እጅግ የከበረ አስገራሚ የእውነት መዝገብ ታጭቆበታል፡፡ ለመነሻ እንዲሆነን አንዱን ቃል መዘን እንመልከት ‹‹ቃልም …››
1. ‹ቃሉ› (ቃልን መረዳት)
ስለዚህ ጉዳይ ልብ መባል ያለበት ጉዳይ አለ፡፡ ይኸውም ቁጥር 1 የሚለውን በጥንቃቄ ካልተረዳን ቁ 14 ምን እንደሚል በትክክል መረዳት አለመቻሉ ነው፡፡ በተለይም ‹ቃል› የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ አስፈላጊነት መረዳት አለብን፡፡ ቃል በቀጥታ ክርስቶስ ማለት ነው፣ እርሱም የእግዚአብሔር ጥበብና ሃይል ነው፣ እግዚአብሔር ለሰው ያለው የግሉ አካላዊ መታየትና መገለጥ ነው፡፡

ከቁጥር 2-13 ለመብራራት እንደተሞከረው የሐዋርያው ሃሳብ ግልጽ ነው፤ ‹‹በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ (ቃልም ከእግዚአብሔር ጋር ነበር /አመት/) ቃልም እግዚአብሔር ነበረ ….ቃልም ሥጋ ሆነ….››
አስቀድመን የዮሐንስ ወንጌል ሲጻፍ በምን ዓላማ እንደተጻፈ ማየት ጠቃሚ ነው፡፡ በዮሐንስ 20.30-31 ‹ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል› በሚለው መሰረት አይሁድ የሆኑትንና ያልሆኑትን ሁለቱንም ወገኖች በጽሁፎቹ ወደ እምነት መምራት ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈበት ዓላማ ነው፡፡ አይሁድን በተመለከተ በእርግጥም ኢየሱስ ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው መሲሁ ክርስቶስ መሆኑን እንዲያምኑ አይሁድ ያልሆኑትን በተመለከተ ደግሞ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እና እግዚአብሔር ወልድ መሆኑን እንዲረዱ ነው፡፡
ሐዋርያው ስለ ኢየሱስ መጻፍ ሲጀምር ዋናውን ሃሳብ እየነካ ለጽሑፉ መግቢያ በሚሰጥበት ጊዜ፣ በዚያው መጠን ግዙፍ ከሆኑ እውነቶች ጋር ይገናኛል፡፡  በመንፈስ ቅዱስ ከተመራ ጥንቃቄ ጋር ‹ክርስቶስ› እና ወይም ‹የእግዚአብሄር ልጅ› የሚሉት ቃላት ለአንባቢዎቹ ከበድ ያሉ ሃሳቦች በመሆናቸው መግቢያው እነዚህን ቃላት ወይም ሐረጎች እንዲያካትት አላደረገም፡፡ ሆኖም ጽሑፉን እየገፋ ሲሄድ ከነዚያ ቃላትና ሃሳቦች መካከል አንዳቸውንም ሊተዋቸው ምንም ፍላጎት አልነበረውም፡፡

አይሁድ የሚጠባበቁት፡- አይሁድ ዮሐንስ “ቃል” እያለ ስለ ክርስቶስ መጻፉን ሲያውቁ በእርግጥም ጆሮአቸውን ይሰጣሉ፡፡ ነገር ግን እነርሱ መሲሁን የሚጠብቁት ከሆነ ምድራዊ ተልእኮ ጋር ከተያያዘ የፖለቲካ ዓላማ ጋር ነበር፡፡ እንግዲህ ዮሐንስ የእነርሱን ጆሮ መግኘቱ እጅግ አስፈላጊ የሚሆነው ኢየሱስ እውነተኛ አምላክ መሆኑን ማወቅ ስላለባቸው ነው፡፡
የአህዛብ ግምት፡- ለአህዛብም ቢሆን ‹የእግዚአብሔር ልጅ› ስለመባሉ  በሚያነቡበት ጊዜ ከአማልክት መካከል አንዱ ከአንዲት ምድራዊት ሴት ጋር ባደረገው ግንኙነት ስለ ተወለደ አንድ ሰው ሊገምቱና ሊስቡ ይችሉ ይሆናል - ይህ አይነቱ አስተሳሰብ በግሪካውያን ተረት  የተለመደ አህዛባዊ አስተሳሰብ ነው፡፡
የዮሐንስ ሸክም፡- ዮሐንስ ሊያስተላልፍ የፈለገው መልዕክት እርሱ የሚጽፍለት “ቃል” የተባለው ሰው ፈጽሞ የተለየና የከበረ መሆኑን አንባቢዎቹ እርግጠኛ ሆነው እንዲረዱ ነው - እርሱ ከብዙዎች አንዱ አይደለም፣ ሌላ መሲህም አይደለም፣ ማንኛውም ክርስቶስ አይደለም፤ በእርግጥም ሌላ የአህዛብ ጣኦት አይደለም፡፡ ለዚህ ነው ሐዋርያው ጌታ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እና የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ማብራራት ከመጀመሩ በፊት ስለ እርሱ የሚጽፍለት “ቃል” የተባለው ይህ ሰው በእውነትና በሙላት ራሱ እግዚአብሔር የመሆኑን ነጥብ በግልጽና በማያሻማ መንገድ እንቅጩን የሚናገረው፡፡
2. የተሳሳተ ግንዛቤን ለማስወገድ የተመረጠ መጠሪያ ‹ቃል›
የሆነ ሆኖ የትኛውንም የተሳሳተ ግንዛቤ ለማስወገድ በመጀመርያ ዋነኛ ማንነቱን በሚገልጥ ስያሜ ይጠራዋል፤ ‹ክርስቶስ› ወይም ‹የእግዚአብሔር ልጅ› ብሎ ሳይሆን በሌላ አይነተኛ ስም ይገልጠዋል፡፡ ዮሐንስ በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ የመረጠው ተገቢ የሆነ ስያሜ ‹ቃል› (በግሪኩ ‹ሎጎስ›) የሚል ነው፡፡
ቃል ለአይሁድ፣ ቃል ለአህዛብ፡- /በአመት የጥናት መግለጫ ‹‹ግሪኮች ‹ቃል› የተሰኘውን የሓሳብ መግለጫ ለተነገረው ፣ ለተሰማው ብቻ ሳይሆን፣ ላልተነገረው ላልተሰማውና ገና በአእምሮ ውስጥ ላለው ሓሳብ ጭምር ይጠቀሙበታል፡፡ ፍጥረተ አለምን በተመለከተ ሲጠቀሙበት ግን የፍጥረትን ሥርዓት የሚመራውን ሕግ በማሰብ ነው፡፡ አይሁድ ግን ‹ቃል› የሚለውን የሓሳብ መግለጫ የሚጠቀሙበት እግዚአብሔርን በተመለከተ ነው፡፡ ስለዚህም ዮሐንስ የተጠቀመው አይሁድም ሆኑ አሕዛብ በሚረዱት ቃል ነው፣››ይላል፡፡/ ለአይሁድም ሆነ ለግሪክ ይህ ቃል ትርጉም የሚሰጥ ነው፡፡ ከሌሎች ቃላት ሁሉ ይልቅ ‹ሎጎስ› ለሁለቱም አይነት አንባቢዎች አዕምሮ ሰፊ ሃሳብን አጭቆ ይዞአል፡፡
ቃል በግሪክ ፍልስፍና ውስጥ፡- በአረማውያን ዘንድ “ሎጎስ” በሚለው ቃል የሚገለጠው ጽንሰ ሃሳብ በእጅጉ ተለመደና የታወቀ ነው፡፡ ግሪካዊው ፈላስፋ ሂራክሊቱስ (600 ቅክ) ሎጎስ የአጥናፍ አለም ነፍስ ነው ብሎ ያስባል- ይኸውም ሁሉም ነገር የተሰራበትና የሆነበት፣ ሁሉንም ነገር ጠብቆ የያዘ፣ እንዲሁም የመላውን ዩኒቨርስ ሚዛን የሚጠብቅ ፈጣሪ ነው ማለት ነው፡፡
የጠቢባኑ ግንዛቤ፡- በዘመኑ ያሉ ጠቢባን ሃሳቡን ሰፋ አድርገው ያዩታል፡፡ ለእነርሱም ሎጎስ በአንድ ጊዜ በሁሉም ስፍራ የሚገኝ (omnipresent) ጥበብ ሲሆን በእርሱም ሁሉ እንደተፈጠረና እንደሚመራ ያስባሉ፡፡
አረማውያን ሎጎስን ከታላቁ አምላክ ጋር ያያይዙታል፡፡ ስለዚህ ዮሐንስ የእርሱ የቃል ምርጫ ለአሕዛባዊ አንባቢዎቹ የሚያረጋግጥላቸው እየጻፈ ያለው ስለ ሁሉን ቻይ እና ለሁሉ ስለሚበቃ፣ የሁሉ ጀማሪ ስለሆነ፣ የሁሉ መሰረትና ምክንያት በመሆን ለራሱ ግን የመሆን ምክንያት ስለሌለው፣ በራሱ የሆነ ስለሆነው ማንነት እንደሆነ ነው፡፡
አይሁድም ፣ ‹ሎጎስ› የሚለው ቃል ከያዘው ጽንሰ ሃሳብ ጋር ጠንካራ የሆነ ግንኙነት አላቸው፡፡ ለእነርሱም የዮሐንስ የመግቢያ ቃላት ማለትም ቁጥር 1 የዘፍጥረትን ‹በመጀመሪያ…› የሚለውን ቃል የሚያስታውሳቸው ነው፡፡ በእርግጥም “ሎጎስ”፣ ወይም “ቃል” የሚለው ጽንሰ ሃሳብ እግዚአብሔር አለምን እንዴት እንደ ፈጠረ ያስታውሳቸዋል፣ ‹‹እግዚአብሔርም አለ›› የሚለው መግለጫ በዘፍጥረት 1 ላይ ዘጠኝ ጊዜ ተጠቅሶአል፡፡  “ሎጎስ” ለአይሁድ በእውነትም የእግዚአብሄር የሆነ “ሁሉን ቻይ ፈጣሪ ቃል” ትርጉም ነው፡፡
የቅዱሳት መጻሕፍት ማስረጃ፡- በመዝሙር 33. 6፣9 ‹‹በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ…..እርሱ ተናግሮአልና፥ ሆኑም እርሱ አዘዘ፥ ጸኑም።›› የሚል እናነባለን፡፡ በኢሳያስ 55. 11 ‹‹ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል የምሻውን ያደርጋል የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም።›› ይላል፡፡ እግዚአብሔር ሲናገር አንድ ነገር እንደሚያደርግና እንደሚሆን እነዚህ ጥቅሶች ግልጽ ያደርጉልናል፡፡ አይሁድ ሎጎስ የተሰኘውን ቃል ከአምላካዊ ተግባር ጋር እንደሚያያይዙት በዚህ ማየት ይቻላል፡፡
ከዚህም በላይ አይሁድ ‹ያህዌ› የተሰኘውን የእግዚአብሔርን ሥም ሲያነሱ፣ ስለ እርሱም በሚናገሩበት ጊዜ፣ ስሙን መጥራት እርሱን እንደ አለማክበር ስለሚቆጥሩ በሌሎች አማራጭ ቃላትና መጠሪያዎች እርሱን መጥራት ይመርጣሉ፡፡ እንደ ‹ቅዱሱ›፣ ‹ስሙ›፣ ወይም ‹ቃል› ያሉትን ይጠቀማሉ፡፡ ስለዚህም  “ቃል” ለአይሁድ ሥነ መለኮት “ያህዌ” ነው፡፡ ዮሐንስ ‹ሎጎስ› የሚለውን ቃል በመጠቀሙ  ለአይሁድ አንባቢያኑ የሚነግራቸው “እኔ የምጽፍለት እርሱ ሃያሉ እና ቅዱሱ የሰማይና የምድር ፈጣሪ ነው”፣ እያለ ነው፡፡
3. የቃሉ መወድስ
ከቁጥር 14 በፊት ባሉት ቁጥሮች ውስጥ ዮሐንስ ስለ ቃሉ የተነገሩ  ወደ 8 የሚደርሱ የመወድስ ዓረፍተ ነገሮችን አስቀምጦአል፣ እያንዳንዳቸውም ለማንኛውም የአይሁድና የግሪክ ሰዎች አስተሳሰብ ተቀባይነት ያላቸው ናቸው፡፡
1ኛ/ ‹በመጀመሪያ ቃል ነበረ› (ቁ 1) በሌላ አባባል፣ ጊዜና ያለው ነገር ሁሉ ወደ መኖር ሲመጣ፣ ቃል ቀድሞውኑ እየኖረ ነበር፡፡ ከዘላለም ጀምሮ እርሱ በዚያ ነበር፡፡ ማንኛውም ነገር ሕልውና ከማግኘቱ በፊት ቃል ነበር፡፡

2ኛ/ ‹ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ›(ቁ 1) ቃሉ ሁልጊዜ ከእግዚአብሄር ጋር ነበረ፡፡ ከዘላለም ሁሉ በፊት በመካከላቸው (በእግዚአብሔርና በቃሉ መካከል) የማይከፈል አንድነት ነበራቸው፡፡

3ኛ/ ‹ቃልም እግዚአብሔር ነበረ›(ቁ 1) አዎ ቃሉ ከእግዚአብሔር ተለይቶ በራሱ ማንነት ይታወቃል፣ ነገር ግን የተፈጠረ ነገር (ፍጡር) አይደለም፡፡ በእርግጥ ከዘላለም በፊት እግዚአብሔር ሆኖ ኖሮአል፡፡ ዮሐንስ እዚህ ላይ በሥላሴዎች መካከል ያለውን ልዩነት በደንብ ይነካል፡፡ ነገር ግን ማናቸውም የማያምኑ የሆኑ አንባቢዎች ይህንን አይረዱትም፡፡

4ኛ/ ‹ሁሉ በእርሱ ሆነ›/ ‹ዓለሙም በእርሱ ሆነ›(ቁ 3ና10) እርሱ የዚህ አጥናፍ አለም (universe) ፈጣሪ ነው፣ የሚለው ዓረፍተ ነገር ለአይሁድም ሆነ ለግሪክ ሰዎች የሚያስቸግራቸው አይደለም፡፡

5ኛ/ ‹በእርሱ ሕይወት ነበረች› (ቁ4) ሕይወት ሰጪ እና የሁሉ ነገር ምንጭ ከሆነው ቃል ህይወትን ያልተቀበለ ሕያው ፍጡር በፍጥረተ ዓለም ውስጥ የለም፡፡ ፍጥረት ሁሉ ሕያው የሆነው በእርሱ ሕይወት ነው፡፡

6ኛ/ ‹ሕይወትም የሰው ብርሐን ነበረች/ ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሐን…›(ቁ4፣9) ከእርሱ የተገኘች ሕይወት ለሰው ልጅ ሁሉ የምታበራ ብርሃን ናት፡፡ ዮሐንስ እዚህ ላይ እየተናገረ ያለው ቃሉ የእግዚአብሔር መገለጠ/ እግዚአብሔርን የሚገልጠው የመሆኑን እውነታ ነው፡፡ ነገር ግን አይሁድ በምሳሌ ምዕራፍ 8 ብርሃን ቃሉን በአካላዊ ማንነቱ እንዳለ ጥበብ ሲመለከቱት አሕዛብ ግን ዓረፍተ ነገሩን በፍልስፍናቸው የተረጉሙታል፡፡

7ኛ/ ‹የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም› (ቁ 11) እዚህ ላይ አንባቢዎቹ ይስማማሉ፣ በእኛ ዘንድ ሁልጊዜ ፈጽሞ የማያስተውሉና የማያስቡ ሞኞች አሉ ይላሉ፡፡

8ኛ/ ያም ሆኖ የሚቀበሉት ደግሞ አሉ ‹ለተቀበሉት…›(ቁ 12) ለሚያምኑበት፣ ለሚቀበሉትና ለሚያመልኩት አንባቢዎቹ በዚህ እንኳን ደስ ያላችሁ ሊባሉና በዚህ ደስ ሊላቸው ገባቸዋል፡፡

በእርግጥም የመጽሐፉን ዋነኛ ገጸ ባህርይ ለአንባቢዎቹ እንዲህ ባለ ተስማሚና ተቀባይነት ባለው አቀራረብ መግቢያ መስጠት የቻለ ጸሐፊ የለም፡፡
ማጠቃለያ
በአዲስ ኪዳን ውስጥ በክርስቶስ መለኮትነት ላይ የተሰጠውን ጠንካራ ትምሀርት እንዳንስተው መጠንቀቅ አለብን፡፡

ስለ እርሱን በተመለከተ  ከገጠሪቱ ናዝሬት እንደ ተነሳ ተራ እንደሆነ አንድ ድንቅ ሰው ማሰብ ሊቀል ይችል ይሆናል፣ በኖረው የፍቅርና ሌሎችን የመንከባከብ ምሳሌ ድንቅ የሆኑ የሕይወት ምሳሌዎችን እና ተሞክሮዎችን እንደተወልን አንድ አስገራሚ ሰው እናየው ይሆናል፡፡ አዎ በእርግጥም ቃሉ በታሪካችን ውስጥ ገብቶ ሥጋ ሆኖአል፣ እኛን መስሎአል፣ ደግሞም ፍጹም ሰው ነበር እስከ አሁንም ድረስ ነው፣ ነገር ግን ሐዋርያው ዮሐንስ በመንፈስ ቅዱስ በመነዳት ከሰጠው ከዚህ ጠንካራ አጽንዖት ውጭ ወንጌላዊ የሆነው አስተምህሮተ ክርስቶሳችን በቀላሉ ሰውን ወደ አማከለ ተራ ደረጃ ማለትም  ከመጽሐፍ ቅዱሳዊው መገለጥ ጋር ፈጽሞ ወደማይታረቅበት ደረጃ ወርዳል፡፡
በመካከለኛው ዘመን ሥነ ጥበብ በተሰሩ፣ ስሜትን የሚነካ የከሳና የገረጣ ፊት ባላቸው ወይም በእጅጉ ተውበው በደመቁ ኃይማኖታዊ በሆኑ ኢየሱሳዊ ሥዕላ ሥዕሎች ላይ የተመሰረተ የዛሬ ስብከት ማንንም ሊያድን አይችልም፡፡ በጣም በእርግጠኝነት መናገር እንደሚቻለው እንዲህ ያለው ሰው ሰራሽ የሆነ “ክርስቶስ” ሐዋርያው ዮሐንስ በወንጌሉም ሆነ በራዕዩ የሚጽፍለት የነገስታት ንጉስና የጌታዎች ጌታ አይደለም፡፡
የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ያቀረቡልን ኢየሱስ እውነተኛ አምላክ፣ ደግሞም ሕያው ሰው መሆኑን በደንብ ማስታወስ አለብን፡፡ ስለዚህም ቃል የተባለው እርሱ የዮሐንስ አህዛባዊ አንባቢዎች ከሚመስላቸው አካል ካልሆነ አንድ መርህ ወይም ሃይል በላይ ያለ በራሱ የሚኖር ማንነት ነው፡፡
ሉቃስም ስለ ሐዋርያቱ ሲናገር ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት (ሉቃ 1.2) በማለት ‹ቃሉ› የሚለውን መግለጫ ይጠቀማል›፣ ፡፡ የሚናገረውው ስለ ጌታ ኢየሱስ ነው ወይንስ ሰለ ወንጌሉ? አንዳንድ ተርጓሚዎች ወንጌሉ ነው ሲሉ ከሁለተኛው ሃሳብ ጋር ቃሉን ለማዛመድ ሞክረዋል፣ ይሁንና ሉቃስ ሐዋርያቱን በተመለከተ ሲናገር ቃሉን ‹በዓይን ያዩት› ናቸው ይላል፣ የሚያመለክተውም ጌታ ኢየሱስን ነው፡፡ ይሁን እንጂ የቃሉ ‹አገልጋዮች› ብሎ ደግሞ ይጠራቸዋል፣ የኸውም ወንጌሉን ያመለክታል፡፡ ሐዋርያቱ ቃሉን ያዩት የቃሉ አገልጋዮች ናቸው፡፡
በጥንት ቤተከክርስቲያን ይህ አከራካሪ ጉዳይ አልነበረም፡፡ ምክንያቱም ለነዚያ ክርስቲያኖች ኢየሱስ ክርስቶስ የተባለው እርሱ በማንነቱ በእርግጥም የወንጌሉ የዘት ነበር፡፡
ይህ በትክክል ጳውሎስ ፤‹መቼም አይሁድ ምልክትን ይለምናሉ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ፥ እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን…› (1ቆሮ 1.22) ብሎ የተናገረለት ጉዳይ ነው፡፡ በገላትያ 3.1 ላይም ‹በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤› ይላል፡፡ስለዚህም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መናገር ማለት ለሐዋርያቱ በእውነትም የስብከታቸውን ይዘት የሚያመለክት ነው፡፡
ዮሐንስ በሚገርም አገላለጽ ይህንን ቃል “የሕይወት ቃል” ሲል ይጠራዋል፣ እርሱንም “ከመጀመሪያው የነበረውን የሰማነው በዓይኖቻችንም ያየነው የተመለከትነው እጆቻችንም የዳሰሱት” ይለዋል ጨምሮም “ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤” ሲል ሐዋርያቱ ከዚያ ቃል ጋር የነበራቸውን ቅርብ ግንኙነት ይመሰክራል፡፡
ከሞት የተነሳውን ሕያው የሆነና የከበረውን ክርስቶስ እያወቀ ያደገ ማንም ሰው ቢሆን፣ ሌላ ማንኛውንም ተራ ነገር ወይም ሌላ ማንንም ቢሆን ፈጽሞ ማወጅና መስበክ አይችልም- እጅግ ያነሰውን የስነ ምግባር መርህ ወይም መልካም ፈቃድን አልያም ደስ የሚል ድምጸት ያላቸውን ጥሩ ጥሩ አዝናኝ አባባሎችን በመስበክና በማወጅ ዘመኑን አያጠፋም፡፡ እንዲህ ላለ ሰብዓዊ ተራ ነገር ሐዋርያቱ ለመሞት አልተዘጋጁም ነበር፣ በእርግጥም እንደ ሰማዕት የሞቱለት ጉዳይ እንዲህ የወረደ ነገር አልነበረም፡፡ እስከሞት ድረስ ሰው ሆኖ በመካከላቸው ከእነርሱ ዘንድ ስላደረው አምላክ ከመናገርና እርሱን ከማምለክ ለአፍታም ቢሆን አላረፉም፡፡ በየዘመናቱ ሁሉ የተሰበከው ደግሞ እንዲሁ ነበር፡፡ አሁንም የሚሰበከው እንዲሁ ነው፡፡ ለዘላለሙም የሚሰበከው እንዲሁ ነው፡፡ አሜን!!

                                                                                 gizachewkr@gmail.com